ደቡብ ግሎባል ባንክ አ.ማ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውን ከዚህ በታች በሠንጠረዡ የተመለከተውን ንብረት በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ሥልጣንና ውክልና መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ተ.ቁ |
የተበዳሪው ስም |
የንብረት አስያዥ ስም |
አበዳሪው ቅርንጫፍ |
ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ |
የቦታው ስፋት |
የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ቁጥር |
የንብረቱ ዓይነት |
የጨረታው መነሻ ዋጋ /ብር/ |
ጨረታ የሚከናወንበት |
|||
ከተማ |
ክ/ከተማ |
ቀበሌ/ወረዳ |
ቀን |
ሰዓት |
||||||||
1 |
ሆፕ የቴሌኮም ምርቶች ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማ |
ብፁህ አቡነ ማቲያስ ንጉሴ ደስታ |
መገናኛ |
አ.አ |
የካ |
02 |
500 ካሬ ሜትር |
የካ266/184000/07 |
ለመኖሪያ(B+G+4 Terrace) |
60,108,167.57 |
ሰኔ 14, 2015 ዓ.ም |
ከጠዋቱ 4፡00-5:30 |
የጨረታ ደንቦች፡-
- ተጫራቾች የጨረታ መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ በደቡብ ግሎባል ባንክ አ.ማ ስም የተሰራ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ) በማስያዝ መመዝገብ ይችላሉ።
- የተጫራቾች ምዝገባ ከጨረታው መዝጊያ ሰዓት ሰላሳ ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል። በጨረታው የመጨረሻ ሰላሳ ደቂቃዎች የተጫራች ምዝገባ አይካሄድም።
- ጨረታው ከላይ በሰንጠረዡ በተገለጸው ቀንና ሰዓት ንብረቱ በሚገኝበት ቅጥር ግቢ ይካሄዳል፡፡
- በጨረታው ላይ ተጫራቾች፣ አስያዥና ተበዳሪ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው መገኘት ይችላሉ፡፡
- የንግድ ማህበራትን ወክሎ ለመጫረት የማህበራቱን መመስረቻ ጽሑፍ የያዘና በማህበራቱ ስም ንብረት ለመግዛት ስልጣን ያለው መሆን ያለበት ሲሆን ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሰነድ በማቅረብ ይሆናል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ መሆኑ በደብዳቤ የተገለጸለት ተጫራች ያሸነፈበትን ዋጋ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ባይከፍል ግን ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፡፡ ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ይመለስላቸዋል፡፡
- በንብረት ማስተላለፍ ሂደት ለመንግስት የሚከፈል ግብር፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የሊዝ ክፍያ ወይም ሌላ ማንኛውንም ክፍያ ገዢው ይከፍላል።
- ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል፡፡
- ለበለጠ ማብራሪያ ደቡብ ግሎባል ባንክ ዋናው መሥሪያ ቤት በስልክ ቁጥር 011 5 31 81 17 (የህግ አገልግሎት መምሪያ) ፣ 011 6 68 68 73 ወይም 011 6 68 63 12 (መገናኛ ቅርንጫፍ) ደውሎ መጠየቅ ወይም አበዳሪውን ቅርንጫፍ በአካል ቀርቦ ማነጋገርና ንብረቱን የሚጎበኙበት ሁኔታ ማመቻቸት ይቻላል።
- ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።